@mariabethania515: uma boa música com bom som Basike Fone de ouvido Bluetooth sem fio com função fone e caixa de som basike 100% original achodo shoppe De 363,00 por 169,99 com 53% off Busque pelo ID CKK-EPA-JAS ou comente quero que mando o link #achaddabBrth #son #música

Beth presente 🎁
Beth presente 🎁
Open In TikTok:
Region: BR
Friday 01 August 2025 13:26:45 GMT
214
0
0
12

Music

Download

Comments

There are no more comments for this video.
To see more videos from user @mariabethania515, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos

የአክሲዮን ማኅበር አደራጆችና መሥራቾች ማንነት፤ መብት እና ኃላፊነት! ********** በኢትዮጵያ የንግድ ሕግ መሠረት አክሲዮን ማህበራት በሁለት መልኩ ሊመሰረቱ ይችላሉ፡፡ አንደኛው መንገድ ማህበሩ ሲመሰረት የማህበሩ አክሲዮን በግልፅ ለህዝብ እንዲሸጥ መግለጫ  በማውጣት እና ካፒታል በመሰብሰብ ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ መግለጫ ሳይወጣ የማህበሩ ካፒታል በመስራቾች ብቻ ሲከፈል እና ሲመሰረት ነው፡፡ እነዚህ የምስረታ ዓይነቶችም በንግድ ህግ ቁጥር 316 እና 317 ላይተመልክተዋል፡፡የማህበሩ አክሲዮኖች ለሕዝብ ሳይሸጡ አክሲዮኖች በመስራቾች የሚገዙስለመሆናቸው ከተፈረመ እና ማህበሩ ከተቋቋመ፣ የመስራቾች ማንነት ጥያቄ አያስነሳም፡፡ ማህበሩ የሚመሰረትበትን ጽሁፍ የፈረሙና የማህበሩን ዋና ገንዘብ ያዋጡ በህግ መስራቾች ናቸው፡፡ ነገር ግን በማህበሩ ያልገቡ ነገር ግን የማህበሩ መቋቋም እንዲፀና ሲሉ ማንኛውንም እርምጃና ለማህበሩ ሥራ ያደረጉ ሁሉ እንደ መስራች እንደሚቆጠሩ በንግድ ህግ ቁጥር 307(4) ላይ ተመልክቷል፡፡ እነዚህ ሰዎች በተለምዶ አደራጆች ተብለው የሚታወቁ ናቸው፡፡ የንግድ ህጉ ግን ለማህበሩ ምስረታ በተለያየ ደረጃ እና ሁኔታ በእውቀት፣ በሙያ ወይም በሃብት አስተዋፅኦ ያደረጉ ሰዎችን በአማርኛ መስራቾች፣ በእንግሊዘኛ “founder” በማለት ይጠራቸዋል፡፡ ነገር ግን ለማህበር ምስረታ አስተዋፅኦ የሚደርጉ ሰዎች፣ የአስተዋፅአቸው ደረጃ የተለያየ ስለሆነ፣ ሁሉም በአንድ ስም መጠራታቸው ተገቢ አይደለም፡፡ አሁን በተግባር በአንዳንድ ማህበራት ምስረታ የምናየውም አደራጅ /promoters/ እና መስራቾች የተለያዩ መሆናቸውን ነው፡፡ ስለዚህ የአክስዮን ማህበራት በሚመሰረቱበት ጊዜ መስራቾች እና አደራጆች መለየት ይገባቸዋል፡፡ አሁን ባለው የንግድ ሀግ ቁጥር 307 መሠረት መስራቾች ሊባሉ የሚችሉት፤ 1. የማህበሩ አክሲየኖች ለሕዝብ የሚሸጡ ከሆነ፣ ማህበሩ የሚመሰረትበትን ፅሁፍ የፈረሙና በሙሉ የማህበሩን ዋና ገንዘብ ያዋጡ ባለአክሲዮኖች፣ 2. የማህበሩ አክሲዮኖች መግለጫ በማውጣት የሚሸጡ ከሆነ - የማህበሩን መግለጫ የፈረሙ፣ - ለማህበሩ በዓይነት መዋጮ ያደረጉ፣ - ከትርፉ ላይ ልዩ ተከፋይነት እንዲኖረው መብት የተሰጣቸው ባለአክሲዮኖች 3. ባለአክሲዮኖች ሳይሆኑ ለማህበሩ መቋቋም ዕቅድ ያወጡ፣ ያስፈፀሙ / Intiated plans or facilitate the formation of the company/ ሰዎች ናቸው፡፡ ከዚህ መረዳት የሚቻለውም በማህበሩ ምስረታ ሂደት በተለያየ ደረጃ የተሳተፉ እና አስተዋፅኦ ያደረጉ ሰዎች በሙሉ የመስራችነት ደረጃ እንዳላቸው ነው፡፡ ነገር ግን ህጉ የአደራጅን እና የመስራችን ፅንሰ ሃሳብ ሳይለይ አጣምሮ የያዘ ስለሆነ ለአፈፃፀም አስቸጋሪ ነው፡፡ በተግባርም ሲያወዛግብ ይታያል፡፡  የቡና ባንክ እና የዘመን ባንክ መስራቾች ከብሔራዊ ባንክ ጋር ገብተው የነበረው ውዝግም የዚሁ መገለጫ ነው፡፡ ሌላው አወዛጋቢ ጉዳይ አክሲዮን ማህበራት መግለጫ ሳያወጡ በባለአክሲዮኖች ብቻ ተመስርተው ከተቋቋሙ እና ህጋዊ ሰውነት ካገኙ በኋላ፣ ተጨማሪ ካፒታል ለማሰባሰብ እና አቅማቸውን ለማሳደግ፣ መግለጫ  በማውጣት አክሲዮን ከሸጡ በኋላ፣ የመመስረቻ ፅሁፋቸውን በማሻሻል አዲሶቹ አክሲዮን ገዥዎች እንዲፈርሙበት ሲደረግ፣ መግለጫውን የፈረሙት አዳዲስ ሰዎች እና አዲስ አክሲዮን በመግዛት የተሻሻለውን መመስረቻ የፈረሙት ሰዎች እንደ መስራች ይቆጠራሉ ወይ? የሚለው ነው፡፡ ማህበሩ ከተመሰረተ እና ህጋዊ ሰውነት ካገኘ በኋላ፣ አዲስ መስራች ህጉስ ይፈቅዳል ወይ የሚለው አከራካሪ ነው፡፡ እንደ እኔ እምነት የማህበሩ የመጀመሪያ አቋቋሚዎች የንግድ ሃሳብ አመንጭተው፣ ጊዜያቸውን እና ገንዘባቸውን አውጥተው መግለጫ  ሳያወጡ ማህበሩን ከመሰረቱ እና ማህበሩም ህጋዊ ሰውነት ካገኘ በኋላ፣ ለማህበሩ ተጨማሪ ካፒታል ለማስገኘት የሚወጣውን መግለጫ /prospectus/ ወይም የተሻሻለ የመመስረቻ ጽሑፍ የሚፈርሙ ሰዎች እንደ መስራች ታይተው የመስራችነት ጥቅም /founders benefit/ ሊከፈላቸው አይገባም፡፡ ለማህበሩ ማሻሻል አስተዋፅኦ የሚያደርጉ ሰዎች ግን ማህበሩ በሚወስነው መሰረት የስራ ዋጋ ሊከፍላቸው ይችላል፡፡ ለእነዚህ ሰዎች የመስራችነት ጥቅም መክፈል ግን ህጉን ይፃረራል፡፡ አሁን እየተሻሻለ ያለው የንግድ ህግ ረቂቅ፣ አሁን ያለውን የህግ ማዕቀፍ ችግሮች በመረዳት አደራጆችን እና መስራቾችን በመለየት እና ትርጉም በመስጠት ደንግጓል፡፡ በረቂቅ ህጉ አንቀጽ 248 (1) መሠረት አደራጅ ማለት አክሲዮኑ ለሕዝብ ክፍት የሆነ ማህበር ምስረታ ያነሳሳ፣ መግለጫ አዘጋጅቶ ሰዎች ማህበሩን እንዲቀላቀሉ የጋበዘ ወይም በአጠቃላይ የማህበሩን ምስረታ ዓላማ አድርጎ ይህንኑ ለማስፈፀም የተንቀሳቀሰና ማህበሩ የማይመሰረት ከሆነ ባለመመስረቱ ምክንያት ለሚመጣ ጉዳት ኃላፊነት የሚወስድ ሰው ነው፡፡ አደራጅ የማህበሩ ባለአክሲዮን የመሆን ግዴታ የሌለበት ሲሆን፣ ከአደራጅ ጋር ባደረገው ውል መሰረት ለማህበሩ ምስረታ አስፈላጊ የሆነ ጥናት፣ የሙያ ድጋፍ እና መሰል አገልግሎት ያቀረበ ባለሙያ አደራጅ እንዳልሆነ በረቂቁ ተመልክቷል፡፡ አሁን ባለው ህግ ላይ ለማህበሩ በዓይነት መዋጮ ያደረጉ እና ከትርፍ ላይ ልዩ ተካፋይነት መብት ያላቸው ባለአክሲዮኖች በህግ መስራች ሲሆን በረቂቁ ላይ ግን ሳይካተቱ ቀርተዋል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት መስራችነት ጥቅም ብቻ ሳይሆን ኃላፊነትም ያለበት ስለሆነ፣ የዚህ ዓይነት ሰዎችን ከሃላፊነት ለማግለል ይመስላል፡፡ ይኹን እንጅ ለማህበር ምስረታ እንደ ቢሮ ወይም ህንፃ ወይም መሬት የመሳሰሉ በዓይነት ተገምተው በመዋጮነት ገቢ የሚያደርጉ ሰዎች ልዩ ጥቅም የማያገኙ ከሆነ የማህበሩ አባል ለመሆን ያላቸውን ተነሳሽነት ይቀንሰዋል፡፡  አንቀጽ 252 ላይ ደግሞ ስለ ማህበሩ መስራቾች ደንግጓል፡፡ የማህበሩ መስራች የሚባሉትም የተወሰኑ ሰዎች ለህዝብ ጥሪ ሳያደርጉ የአክሲዮን ማህበር ምስረታን የተመለከቱ የህግ ድንጋጌዎች በማሟላት በመካከላቸው የአክሲዮን ማህበር ያቋቁሙ ማህበርተኞች ናቸው፡፡ ከረቂቅ ህጉ መረዳት እንደሚቻለው፣ አደራጆች የሚኖሩት ማህበሩ የሚመሰረተው መግለጫ በማውጣት /Public subscription/ ሲሆን፣ መስራቾች የሚኖሩት ደግሞ የህዝብ መግለጫ prospectus/ ሳይወጣ፣ ማህበሩ በማህበርተኞች ብቻ ሲመሰረት እንደሆነ ነው፡፡ ነገር ግን ማህበሩ የህዝብ መግለጫ ሳያወጣ በተወሰኑ ማህበርተኞች ብቻ ከተመሰረተ እና ከተመዘገበ በኋላ፣ ተጨማሪ ካፒታል ለመሳብ የህዝብ መግለጫ ቢያወጣ እና የተሻሻለ የመመስረቻ ጽሑፍ ቢፈረም፣ ይህንን መግለጫ /prospectus/ እና የተሻሻለውን መስረቻ አዲስ ገቢዎች አደራጅ ይባላሉ ወይ የሚለውን አዲሱ ረቂቅ የንግድ ህግም አይመልስም፡፡ ስለዚህ የንግድ ህጉ ከመፅደቁ በፊት ይህንን ነጥብም በሚመልስ መልኩ ቢሻሻል ጠቃሚ ይሆናል፡፡ የማህበሩ መስራቾች ግዴታና ኃላፊነት መስራችነት ጥቅም የሚያስገኝ ተግባር ቢሆንም ኃላፊነትም ያለበት ነው፡፡ የመስራቾች ወይም አደራጆች ዋና ግዴታ የምስረታ ሂደቱን ውጤታማ ማድረግ ሲሆን፣ ዋና ዋና ተግባሮችም፤ አክሲዮን መሸጥ፣ ካፒታል መሰብሰብ፣ የመመስረቻ እና መተዳደሪያ ደንብ ማርቀቅ፣ በዓይነት የሚገመቱ መዋጮዎች በአግባቡ ማስገመት፣ የፈራሚዎች ጉባኤ ማዘጋጀት፣ ኩባንያውን ማስመዝገብ፣የስራ ቦታዎችን ማዘጋጀት፣ አስፈላጊ የሰው ኃይል ማሟላትን ያካትታል፡፡
የአክሲዮን ማኅበር አደራጆችና መሥራቾች ማንነት፤ መብት እና ኃላፊነት! ********** በኢትዮጵያ የንግድ ሕግ መሠረት አክሲዮን ማህበራት በሁለት መልኩ ሊመሰረቱ ይችላሉ፡፡ አንደኛው መንገድ ማህበሩ ሲመሰረት የማህበሩ አክሲዮን በግልፅ ለህዝብ እንዲሸጥ መግለጫ በማውጣት እና ካፒታል በመሰብሰብ ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ መግለጫ ሳይወጣ የማህበሩ ካፒታል በመስራቾች ብቻ ሲከፈል እና ሲመሰረት ነው፡፡ እነዚህ የምስረታ ዓይነቶችም በንግድ ህግ ቁጥር 316 እና 317 ላይተመልክተዋል፡፡የማህበሩ አክሲዮኖች ለሕዝብ ሳይሸጡ አክሲዮኖች በመስራቾች የሚገዙስለመሆናቸው ከተፈረመ እና ማህበሩ ከተቋቋመ፣ የመስራቾች ማንነት ጥያቄ አያስነሳም፡፡ ማህበሩ የሚመሰረትበትን ጽሁፍ የፈረሙና የማህበሩን ዋና ገንዘብ ያዋጡ በህግ መስራቾች ናቸው፡፡ ነገር ግን በማህበሩ ያልገቡ ነገር ግን የማህበሩ መቋቋም እንዲፀና ሲሉ ማንኛውንም እርምጃና ለማህበሩ ሥራ ያደረጉ ሁሉ እንደ መስራች እንደሚቆጠሩ በንግድ ህግ ቁጥር 307(4) ላይ ተመልክቷል፡፡ እነዚህ ሰዎች በተለምዶ አደራጆች ተብለው የሚታወቁ ናቸው፡፡ የንግድ ህጉ ግን ለማህበሩ ምስረታ በተለያየ ደረጃ እና ሁኔታ በእውቀት፣ በሙያ ወይም በሃብት አስተዋፅኦ ያደረጉ ሰዎችን በአማርኛ መስራቾች፣ በእንግሊዘኛ “founder” በማለት ይጠራቸዋል፡፡ ነገር ግን ለማህበር ምስረታ አስተዋፅኦ የሚደርጉ ሰዎች፣ የአስተዋፅአቸው ደረጃ የተለያየ ስለሆነ፣ ሁሉም በአንድ ስም መጠራታቸው ተገቢ አይደለም፡፡ አሁን በተግባር በአንዳንድ ማህበራት ምስረታ የምናየውም አደራጅ /promoters/ እና መስራቾች የተለያዩ መሆናቸውን ነው፡፡ ስለዚህ የአክስዮን ማህበራት በሚመሰረቱበት ጊዜ መስራቾች እና አደራጆች መለየት ይገባቸዋል፡፡ አሁን ባለው የንግድ ሀግ ቁጥር 307 መሠረት መስራቾች ሊባሉ የሚችሉት፤ 1. የማህበሩ አክሲየኖች ለሕዝብ የሚሸጡ ከሆነ፣ ማህበሩ የሚመሰረትበትን ፅሁፍ የፈረሙና በሙሉ የማህበሩን ዋና ገንዘብ ያዋጡ ባለአክሲዮኖች፣ 2. የማህበሩ አክሲዮኖች መግለጫ በማውጣት የሚሸጡ ከሆነ - የማህበሩን መግለጫ የፈረሙ፣ - ለማህበሩ በዓይነት መዋጮ ያደረጉ፣ - ከትርፉ ላይ ልዩ ተከፋይነት እንዲኖረው መብት የተሰጣቸው ባለአክሲዮኖች 3. ባለአክሲዮኖች ሳይሆኑ ለማህበሩ መቋቋም ዕቅድ ያወጡ፣ ያስፈፀሙ / Intiated plans or facilitate the formation of the company/ ሰዎች ናቸው፡፡ ከዚህ መረዳት የሚቻለውም በማህበሩ ምስረታ ሂደት በተለያየ ደረጃ የተሳተፉ እና አስተዋፅኦ ያደረጉ ሰዎች በሙሉ የመስራችነት ደረጃ እንዳላቸው ነው፡፡ ነገር ግን ህጉ የአደራጅን እና የመስራችን ፅንሰ ሃሳብ ሳይለይ አጣምሮ የያዘ ስለሆነ ለአፈፃፀም አስቸጋሪ ነው፡፡ በተግባርም ሲያወዛግብ ይታያል፡፡ የቡና ባንክ እና የዘመን ባንክ መስራቾች ከብሔራዊ ባንክ ጋር ገብተው የነበረው ውዝግም የዚሁ መገለጫ ነው፡፡ ሌላው አወዛጋቢ ጉዳይ አክሲዮን ማህበራት መግለጫ ሳያወጡ በባለአክሲዮኖች ብቻ ተመስርተው ከተቋቋሙ እና ህጋዊ ሰውነት ካገኙ በኋላ፣ ተጨማሪ ካፒታል ለማሰባሰብ እና አቅማቸውን ለማሳደግ፣ መግለጫ በማውጣት አክሲዮን ከሸጡ በኋላ፣ የመመስረቻ ፅሁፋቸውን በማሻሻል አዲሶቹ አክሲዮን ገዥዎች እንዲፈርሙበት ሲደረግ፣ መግለጫውን የፈረሙት አዳዲስ ሰዎች እና አዲስ አክሲዮን በመግዛት የተሻሻለውን መመስረቻ የፈረሙት ሰዎች እንደ መስራች ይቆጠራሉ ወይ? የሚለው ነው፡፡ ማህበሩ ከተመሰረተ እና ህጋዊ ሰውነት ካገኘ በኋላ፣ አዲስ መስራች ህጉስ ይፈቅዳል ወይ የሚለው አከራካሪ ነው፡፡ እንደ እኔ እምነት የማህበሩ የመጀመሪያ አቋቋሚዎች የንግድ ሃሳብ አመንጭተው፣ ጊዜያቸውን እና ገንዘባቸውን አውጥተው መግለጫ ሳያወጡ ማህበሩን ከመሰረቱ እና ማህበሩም ህጋዊ ሰውነት ካገኘ በኋላ፣ ለማህበሩ ተጨማሪ ካፒታል ለማስገኘት የሚወጣውን መግለጫ /prospectus/ ወይም የተሻሻለ የመመስረቻ ጽሑፍ የሚፈርሙ ሰዎች እንደ መስራች ታይተው የመስራችነት ጥቅም /founders benefit/ ሊከፈላቸው አይገባም፡፡ ለማህበሩ ማሻሻል አስተዋፅኦ የሚያደርጉ ሰዎች ግን ማህበሩ በሚወስነው መሰረት የስራ ዋጋ ሊከፍላቸው ይችላል፡፡ ለእነዚህ ሰዎች የመስራችነት ጥቅም መክፈል ግን ህጉን ይፃረራል፡፡ አሁን እየተሻሻለ ያለው የንግድ ህግ ረቂቅ፣ አሁን ያለውን የህግ ማዕቀፍ ችግሮች በመረዳት አደራጆችን እና መስራቾችን በመለየት እና ትርጉም በመስጠት ደንግጓል፡፡ በረቂቅ ህጉ አንቀጽ 248 (1) መሠረት አደራጅ ማለት አክሲዮኑ ለሕዝብ ክፍት የሆነ ማህበር ምስረታ ያነሳሳ፣ መግለጫ አዘጋጅቶ ሰዎች ማህበሩን እንዲቀላቀሉ የጋበዘ ወይም በአጠቃላይ የማህበሩን ምስረታ ዓላማ አድርጎ ይህንኑ ለማስፈፀም የተንቀሳቀሰና ማህበሩ የማይመሰረት ከሆነ ባለመመስረቱ ምክንያት ለሚመጣ ጉዳት ኃላፊነት የሚወስድ ሰው ነው፡፡ አደራጅ የማህበሩ ባለአክሲዮን የመሆን ግዴታ የሌለበት ሲሆን፣ ከአደራጅ ጋር ባደረገው ውል መሰረት ለማህበሩ ምስረታ አስፈላጊ የሆነ ጥናት፣ የሙያ ድጋፍ እና መሰል አገልግሎት ያቀረበ ባለሙያ አደራጅ እንዳልሆነ በረቂቁ ተመልክቷል፡፡ አሁን ባለው ህግ ላይ ለማህበሩ በዓይነት መዋጮ ያደረጉ እና ከትርፍ ላይ ልዩ ተካፋይነት መብት ያላቸው ባለአክሲዮኖች በህግ መስራች ሲሆን በረቂቁ ላይ ግን ሳይካተቱ ቀርተዋል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት መስራችነት ጥቅም ብቻ ሳይሆን ኃላፊነትም ያለበት ስለሆነ፣ የዚህ ዓይነት ሰዎችን ከሃላፊነት ለማግለል ይመስላል፡፡ ይኹን እንጅ ለማህበር ምስረታ እንደ ቢሮ ወይም ህንፃ ወይም መሬት የመሳሰሉ በዓይነት ተገምተው በመዋጮነት ገቢ የሚያደርጉ ሰዎች ልዩ ጥቅም የማያገኙ ከሆነ የማህበሩ አባል ለመሆን ያላቸውን ተነሳሽነት ይቀንሰዋል፡፡ አንቀጽ 252 ላይ ደግሞ ስለ ማህበሩ መስራቾች ደንግጓል፡፡ የማህበሩ መስራች የሚባሉትም የተወሰኑ ሰዎች ለህዝብ ጥሪ ሳያደርጉ የአክሲዮን ማህበር ምስረታን የተመለከቱ የህግ ድንጋጌዎች በማሟላት በመካከላቸው የአክሲዮን ማህበር ያቋቁሙ ማህበርተኞች ናቸው፡፡ ከረቂቅ ህጉ መረዳት እንደሚቻለው፣ አደራጆች የሚኖሩት ማህበሩ የሚመሰረተው መግለጫ በማውጣት /Public subscription/ ሲሆን፣ መስራቾች የሚኖሩት ደግሞ የህዝብ መግለጫ prospectus/ ሳይወጣ፣ ማህበሩ በማህበርተኞች ብቻ ሲመሰረት እንደሆነ ነው፡፡ ነገር ግን ማህበሩ የህዝብ መግለጫ ሳያወጣ በተወሰኑ ማህበርተኞች ብቻ ከተመሰረተ እና ከተመዘገበ በኋላ፣ ተጨማሪ ካፒታል ለመሳብ የህዝብ መግለጫ ቢያወጣ እና የተሻሻለ የመመስረቻ ጽሑፍ ቢፈረም፣ ይህንን መግለጫ /prospectus/ እና የተሻሻለውን መስረቻ አዲስ ገቢዎች አደራጅ ይባላሉ ወይ የሚለውን አዲሱ ረቂቅ የንግድ ህግም አይመልስም፡፡ ስለዚህ የንግድ ህጉ ከመፅደቁ በፊት ይህንን ነጥብም በሚመልስ መልኩ ቢሻሻል ጠቃሚ ይሆናል፡፡ የማህበሩ መስራቾች ግዴታና ኃላፊነት መስራችነት ጥቅም የሚያስገኝ ተግባር ቢሆንም ኃላፊነትም ያለበት ነው፡፡ የመስራቾች ወይም አደራጆች ዋና ግዴታ የምስረታ ሂደቱን ውጤታማ ማድረግ ሲሆን፣ ዋና ዋና ተግባሮችም፤ አክሲዮን መሸጥ፣ ካፒታል መሰብሰብ፣ የመመስረቻ እና መተዳደሪያ ደንብ ማርቀቅ፣ በዓይነት የሚገመቱ መዋጮዎች በአግባቡ ማስገመት፣ የፈራሚዎች ጉባኤ ማዘጋጀት፣ ኩባንያውን ማስመዝገብ፣የስራ ቦታዎችን ማዘጋጀት፣ አስፈላጊ የሰው ኃይል ማሟላትን ያካትታል፡፡

About